የሀገር ውስጥ ዜና

በአዲስ አበባ የተከሰተው ጭጋጋማ የአየር ሁኔታ የአውሮፕላን በረራዎችን አስተጓጎለ

By Tibebu Kebede

August 04, 2020

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 28፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በዛሬው ጭጋጋማ የአየር ሁኔታ ሳቢያ በአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ሊያርፉ የነበሩ አውሮፕላኖች በሌሎች የአውሮፕላን ማረፊያዎች እንዲያርፉ ተደረገ።

በዛሬው እለት በአዲስ አበባ ላይ ከፍተኛ የሆነ ጭጋጋማ የአየር ሁኔታ የተስተዋለ ሲሆን፥ አብዛኛው የከተማዋ ክፍልም በጉም ተሸፍኖ ነው የዋለው።