ቢዝነስ

በደቡብ ክልል በ2012 በጀት አመት 9 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር ካፒታል ላስመዘገቡ ፕሮጀክቶች ፈቃድ መሰጠቱ ተገለፀ

By Tibebu Kebede

August 05, 2020

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 29፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በ2012 በጀት አመት ከ9 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር ካፒታል ላስመዘገቡ የሀገር ውስጥ ባለሀብቶችና ዳያስፖራዎች በግልና በአክሲዮን ፈቃድ መሰጠቱን የደቡብ ክልል ኢንቨስትመንት ኮሚሽን አስታወቀ።

ኮሚሽኑ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳስታወቀው በክልሉ የሰላምና ጸጥታ ሁኔታ እየተሻሻለ በመምጣቱ የኢንቨስትመንት ፍሰቱም እድገት እያሳየ መምጣቱን ነው ያስታወቀው፡፡