የሀገር ውስጥ ዜና

በአፋር ክልል የአዋሽ ወንዝ በመሙላቱ 32 ሺህ ሰዎች ተፈናቀሉ

By Tibebu Kebede

August 05, 2020

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 29፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአፋር ክልል የአዋሽ ወንዝ ሞልቶ በተለያዩ ወረዳዎች 32 ሺህ ሰዎች መፈናቀላቸዉን የክልሉ አደጋ መከላከልና ምግብ ዋሰትና ማስተባባሪያ ጽህፈት ቤት ገለፀ ።

በአፋር ክልል ክረምቱን ተከትሎ እየጣለ ባለው ዝናብ የአዋሽ ወንዝ ሞልቶ በ6 ወረዳዎች 32 ሺህ ሰዎች መፈናቀላቸውን በፅህፈት ቤቱ የቅድመ ማስጠንቀቂያና ፈጣን ምላሽ ዳይሬክተር አቶ አይዳሂስ ያሲን ገልፀዋል ።