አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 30 ፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የታላቁ የህዳሴ ግድብ የመጀመሪያ የውሃ ሙሌት መከናወን ህዝቡን ለተሻለ ተሳትፎ ማነሳሳቱን የኦሮሚያ እና የአማራ የክልል የህዳሴ ግድብ ህዝባዊ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤቶች ገለጹ።
ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ቆይታ ያደረጉ የኦሮሚያ እና የአማራ ክልል ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት አመራሮች ÷ከግድቡ የመጀመሪያ የውሃ ሙሌት በኋላ የህዝቡ የቦንድ ግዚ እና የ8100 ተሳትፎ ተጠናክሮ መቀጠሉን ተናግረዋል።