የሀገር ውስጥ ዜና

የሃይማኖት መሪዎች ነገ የሚጀመረውን ጾመ ፍልሰታ ምክንያት በማድረግ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ

By Meseret Demissu

August 06, 2020

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 30፣2012 ( አኤፍ.ቢ.ሲ) የሃይማኖት መሪዎች ነሀሴ አንድ ተጀምሮ ለሚቀጥሉት ሁለት ሳምንታት የሚቆየውን ጾመ ፍልሰታ ምክንያት በማድረግ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ÷ከነሐሴ አንድ ቀን ጀምሮ እስከ ነሐሴ እኩሌታ ለሚጾመው ጾመ ፍልሰታ እንኳን አደራሳችሁ ብለዋል።