አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 3፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ባለፉት ሁለት ወራት ከ600 በላይ የአቅመ ደካማ ቤቶች ከበጎ ፈቃደኛ ወገኖች ጋር በመሆን መጠገናቸውን ኢንጂነር ታከለ ኡማ አስታወቁ፡፡
የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ በፌስቡክ ገፃቸው ባሰፈሩት ፅሁፍ እንዳስታወቁት ከበጎ ፈቃደኛ ወገኖች ጋር በመሆን ባለፉት ሁለት ወራት ከ600 በላይ የሚሆኑ የአቅመ ደካማ ቤቶች የተጠገኑ ሲሆን÷ ዛሬም ብዙዎች የኛንና የናንተን ድጋፍ ይፈልጋሉ ብለዋል።