ኮሮናቫይረስ

በኢትዮጵያ በ24 ሰዓታት 565 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ሲገኝባቸው፤ የ17 ሰዎች ሕይወት አልፏል

By Meseret Demissu

August 09, 2020

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 3፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 9 ሺህ 035 የላብራቶሪ ምርመራ 565 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።

በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 22 ሺህ 818 መድረሱንም የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ ባወጡት መረጃ አመላክተዋል።