የሀገር ውስጥ ዜና

በደቡብ ክልል የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች 160 ሺህ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ እድል ፈጥረዋል

By Feven Bishaw

August 10, 2020

አዲስ አበባ፣ ነሀሴ 4 ፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ)በደቡብ ክልል ወደ ተግባር የገቡ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች 160 ሺህ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ እድል መፍጠራቸው ተገለጸ፡፡

የክልሉ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን እንደገለጸው÷ በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች በልዩ ልዩ የስራ መስኮች ተሰማርተው የሚገኙ ከ2 ሺህ በላይ የሚሆኑ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች 159 ሺህ 562 ለሚሆኑ ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የስራ እድል ፈጥረዋል።