አዲስ አበባ፣ ነሀሴ 4 ፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ)ህገ ወጥ የጦር መሳሪያ ዝውውርን ለመከላከል ሲባል የጦር መሳሪያ ምዝገባ ለማድረግ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የሰላም ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል አስታወቁ፡፡
ኢትዮጵያ ህገ ወጥ የጦር መሳሪያን ለመቆጣጠርና ለማስተዳደር በወጣው በአዋጅ ላይ የጦር መሳሪያ ያላቸው ዜጎች የጦር መሳሪያቸውን ህጋዊ ለማድርግ በሁለት ዓመት ውስጥ ማስመዝገብ ይኖርባቸዋል።