አዲስ አበባ፣ ነሀሴ 4 ፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወርዳ 4 ጎተራ ኮንዶሚኒየም ውስጥ 108 ማህተሞች እና የተለያዩ ሀሰተኛ ሰነዶችን ለተለያዩ ህገ ወጥ ተግባራት ሲጠቀሙ የነበሩ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሰር መዋሉን ፖሊስ ገለጸ።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ባወጣው መረጃ እንዳስታወቀው፥ ወንጀሉን በመፈፀም የተጠረጠሩት ሁለት ግለሰቦች ሀምሌ 1 ቀን 2012 ዓ.ም ነው በቁጥጥር ስር የዋሉት።