የሀገር ውስጥ ዜና

በቂርቆስ ክ/ከተማ 108 ማህተሞችና ሀሰተኛ ሰነዶችን ለህገ ወጥ ተግባራት ሲጠቀሙ የነበሩ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሰር ዋሉ

By Tibebu Kebede

August 10, 2020

አዲስ አበባ፣ ነሀሴ 4 ፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወርዳ 4 ጎተራ ኮንዶሚኒየም ውስጥ 108 ማህተሞች እና የተለያዩ ሀሰተኛ ሰነዶችን ለተለያዩ ህገ ወጥ ተግባራት ሲጠቀሙ የነበሩ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሰር መዋሉን ፖሊስ ገለጸ።

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ባወጣው መረጃ እንዳስታወቀው፥ ወንጀሉን በመፈፀም የተጠረጠሩት ሁለት ግለሰቦች ሀምሌ 1 ቀን 2012 ዓ.ም ነው በቁጥጥር ስር የዋሉት።