የሀገር ውስጥ ዜና

በአማራ ክልል ከ4 ነጥብ 2 ሚሊየን በላይ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ተሰራጭቷል

By Feven Bishaw

August 10, 2020

አዲስ አበባ ፣ ነሀሴ 4 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በአማራ ክልል በ2012 የበጀት አመት 4 ነጥብ 2 ሚሊየን በላይ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ መሰራጨቱን የክልሉ ኀብረት ሥራ ማኅበራት ማስፋፊያ ኤጀንሲ አስታወቀ፡፡

በክልሉ በበጀት ዓመቱ 6 ሚሊየን 111 ሺህ 561 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ለማሰራጨት ታቅዶ የነበረ ሲሆን እስካሁን ወደ መጋዘን የገባው 5 ሚሊየን 282 ሺህ 774 ኩንታል ወይም ከእቅዱ 86 ነጥብ 4 በመቶ መሆኑን ኢጀንሲው አስታውቋል፡፡