የሀገር ውስጥ ዜና

ለሁለት ቀናት የተካሄደው የአማራ ብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ኮንፈረንስ ተጠናቀቀ

By Tibebu Kebede

August 12, 2020

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 6፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአማራ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ለሁለት ቀን ያካሄደውን የከፍተኛ አመራሮች ውይይት መጠናቀቁንና በውይይቱ የተነሱ ጉዳዮች አስመልክቶ መግለጫ ሰጥቷል።

የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ አገኘሁ ተሻገር በሰጡት መግለጫ ፓርቲው በሁለት ዓመት የለውጥ ጉዞ ፣ ብልፅግና ፓርቲ ከመምጣቱ በፊትና ከመጣ በኋላ ስለመጣው ለውጥ መወያየቱን ገልፀዋል።