አዲስ አበባ፣ ነሀሴ 7፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአዲስ አበባ በኮሮና ቫይረስ ስርጭት ሳቢያ የኑሮ ችግር ሊገጥማቸው የሚችሉ ዜጎችን ለመታደግ የሚከናወነውን የገቢ ማሰባሰብ ስራ ለማጠናከር የሚያስችል ስልት መዘጋጀቱን የከተማው አስተዳደር የማህበራዊ ትረስት ፈንድ ጽህፈት ቤት ገለጸ።
የጽህፈት ቤቱ ሀላፊ ወይዘሮ ፍቅርተ ነጋሽ እንደገለጹት፥ በከተማው አስተዳደር በቀረበው ጥሪ መሰረት በመዲናዋ በኮሮና ቫይረስ ስርጭት ሳቢያ የኑሮ ችግር ሊገጥማቸው የሚችሉ ዜጎችን ለመታደግ የድጋፍ ማሰባሰብ ስራው ሲከናወን ቆይቷል።