አዲስ አበባ፣ ነሀሴ 7፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የታላቁየኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የመጀመሪያ ዙር የውሃ ሙሌት መካሄድን ተከትሎ ለግድቡ የሚደረገው የገንዘብና ፖለቲካዊ ድጋፍ መጨመሩን የግድቡ ህዝባዊ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ምክር ቤት ጽህፈት ቤት ገለፀ።
ከመሰረተ ድንጋይ መቀመጥ ማግስት የጀመረው ድጋፍ ለ9 ዓመታት መቀጠሉን በታለቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ህዝባዊ ተሳትፎ ማስተባባሪያ ምክር ቤት ጽህፈት ቤት የህዝብ ግንኙነት ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሀይሉ አብርሃም ይናገራሉ።