የሀገር ውስጥ ዜና

ፍርድ ቤቱ አቶ ጃዋር መሀመድን ጨምሮ በ14 ተጠርጣሪዎች ላይ የአቃቤ ህግ የቅድመ ምርመራ ምስክሮችን ለመስማት ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጠ

By Tibebu Kebede

August 13, 2020

አዲስ አበባ፣ ነሀሴ 7፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ፍርድ ቤቱ አቶ ጃዋር መሀመድን ጨምሮ በ14 ተጠርጣሪዎች ላይ የአቃቤ ህግ የቅድመ ምርመራ ምስክሮችን ለመስማት ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጠ።

በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት በልደታ አዳራሽ አቶ ጃዋር መሀመድን ጨምሮ በ14 ተጠርጣሪዎች መዝገብ የአቃቤ ህግ የቅድመ ምርመራ ምስክሮችን ለመስማት ችሎት ተሰይሞ የነበረ ቢሆንም፥ አምስት ተጠርጣሪዎች ከህክምና ጋር በተያያዘ ስላልቀረቡ እነሱ በሌሉበት ምስክሮች ሊሰሙ አይገባም የሚል አቤቱታን ተጠርጣሪዎቹ አቅርበው ነበር።