ቢዝነስ

የኮሮና ቫይረሰ በአምራች ሃይሉ ላይ ጉዳት እንዳያደርስ ትኩረት ሊደረግ ይገባል- የምጣኔ ሀብት ባለሙያዎች

By Tibebu Kebede

August 13, 2020

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 7፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኮሮና ቫይረሰ በአምራች ሃይሉ ላይ ከፍ ያለ ጉዳት እንዳያደርስ ትኩረት ሊደረግ እንደሚገባ የምጣኔ ሃብት ባለሙያዎች አስታወቁ።

ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ቆይታ ያደረጉ የምጣኔ ሃብት ባለሙያዎች፥ የቫይረሱ ስርጭት ተጽእኖ በምጣኔ ሃብቱ ላይ ከፍ ያለ ጉዳት እንዳያደርስ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባ አንሰተዋል።