አዲስ አበባ ፣ ነሃሴ 9፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ እያደገ የመጣውን የደንበኞች ፍላጎት ለሟሟላት በሚበርባቸው የሀገር ውስጥ መዳረሻዎቹ የበረራ ቁጥር መጨመሩን አስታወቀ።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት በላከው መግለጫ እያደገ የመጣውን የደንበኞች የጉዞ ፍላጎት ለሟሟላት በሀገር ውስጥ መዳረሻዎቹ በሚሰጠው ሳምንታዊ መደበኛ የበረራ አገልግሎት ላይማሻሻያ ማድረጉን ነው ያስታወቀው።