ቢዝነስ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሚበርባቸው የሀገር ውስጥ መዳረሻዎቹ የበረራ ቁጥር ጨመረ

By Tibebu Kebede

August 15, 2020

አዲስ አበባ ፣ ነሃሴ 9፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ እያደገ የመጣውን የደንበኞች ፍላጎት ለሟሟላት በሚበርባቸው የሀገር ውስጥ መዳረሻዎቹ የበረራ ቁጥር መጨመሩን አስታወቀ።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት በላከው መግለጫ እያደገ የመጣውን የደንበኞች የጉዞ ፍላጎት ለሟሟላት በሀገር ውስጥ መዳረሻዎቹ በሚሰጠው ሳምንታዊ መደበኛ የበረራ አገልግሎት ላይማሻሻያ ማድረጉን ነው ያስታወቀው።