የሀገር ውስጥ ዜና

የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ሲጠናቀቅ ለቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚያስገኘውን ሠፊ የልማት ዕድል ለመጠቀም ዝግጅት እየተደረገ መሆኑ ተገለፀ

By Tibebu Kebede

August 18, 2020

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 12፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ሲጠናቀቅ ለቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከሚያስገኘው ዘርፈ-ብዙ የመጠቀም ዕድል የክልሉን ሕዝብ ተጠቃሚ ለማድረግ የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታሁን አብዲሳ ተናገሩ፡፡

የታላቁ የሕዳሴ ግድብ ግንባታ ሲጠናቀቅ በሚፈጠረው “የሕዳሴ ኃይቅ” ዙሪያ የሚከናወኑ የተለያዩ የልማት ሥራዎችን ያካተተ ክልላዊ የ5 ዓመት ስትራቴጂክ ረቂቅ ዕቅድ ላይ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ውይይት አካሂደዋል፡፡