የሀገር ውስጥ ዜና

በፈረንጆቹ 2020 ሊጎበኙ ከሚገባቸው 50 የዓለማችን ቦታዎች መካከል አዲስ አበባ አንዷ ሆናለች

By Tibebu Kebede

December 18, 2019

አዲስ አበባ ታህሳስ 8፣ 2012 (ኤፍቢሲ) በዓለም ላይ ታዋቂ የጉዞ መረጃ አውጪ ድረገፅ የሆነው ትራቨል ኤንድ ሌይዠር የተባለው ድረገፅ በፈረንጆቹ 2020 ሊጎበኙ ከሚገባቸው 50 የዓለማችን ስፍራዎች ውስጥ አዲስ አበባን አንደኛ አደርጎ አስቀምጣል።

የዘንድሮውን የሰላም ኖቤል ሽልማት የተቀበሉት የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በቤተመንግስት አስገንብተው በቅርቡ ለህዝብ ክፍት ያደረጉት አንድነት ፓርክ የከተማዋ አዲስ ገፅታ መሆኑን ድረገፁ አስነብቧል።