የሀገር ውስጥ ዜና

ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት በተጠረጠሩበት ወንጀል ዐቃቤ ህግ በ10 ቀን ውስጥ ክስ እንዲመሰርት ብይን ተሰጠ

By Tibebu Kebede

August 19, 2020

አዲስ አበባ ፣ ነሀሴ 13 ፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት በተጠረጠሩበት ሁከትና አመጽ በማስነሳት በሰውና በንብረት ላይ ጉዳት ማድረስ ወንጀል አቃቤ ህግ በ10 ቀን ውስጥ ክስ እንዲመሰርት ብይን ተሰጠ፡፡

መርማሪ ፖሊስ በኢኒጂነር ይልቃል ላይ ሲያከናውን የነበረውን ምርመራ ማጠናቀቁን እና መዝገቡንም ለዐቃቤ ህግ መስጠቱን ለችሎቱ ገልጿል፡፡