የሀገር ውስጥ ዜና

አቶ ሽመልስ አብዲሳ በምስራቅ ሸዋ የሚከናወነውን የመልሶ ማቋቋም እንቅስቃሴ ጎበኙ

By Meseret Demissu

August 20, 2020

አዲስ አበባ ፣ ነሐሴ 14 ፣ 2012 (ኤፍ. ቢ.ሲ) በኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ የተመራ ልዑክ ባለፈው ሰሞን በነበረው ሁከትና ግርገር የተጎዳውን ንብረት መልሶ የማቋቋሙ ስራ በምን ደረጃ ላይ እንዳለ ጎብኝቷል።

የፕሬዝዳንቱ ጉብኝት የክልሉን መንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችን ያካተተ ሲሆን÷ ጉብኝቱ በምስራቅ ሸዋ ባቱ፣ አርሲ ነገሌና ሻሸመኔን ጨምሮ የምዕራብ አርሲ፣ አርሲ እንዲሁም ባሌን ያካተተ መሆኑ ተገልጿል ።