አዲስ አበባ ፣ ነሃሴ 14 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በሻሸመኔ ከተማ የውስጥ ለውስጥ የጸጥታ ስራን በማከወን ላይ በነበሩ ጸጥታ አስከባሪዎች ላይ ቦምብ በወረወረ የኦነግ ሸኔ አባል ላይ እርምጃ መወሰዱን ፖሊስ ገለፀ።
ዛሬ ከጠዋቱ አንድ ሰአት ተኩል አከባቢ በሻሸመኔ ከተማ 01 ወይም አዋሾ ቀበሌ አካባቢ የጸጥታ ሀይሎች አካባቢያዊ ዳሳሳ ቅኝት ሲያደርጉ ነው ከድር ቱሌ የተባለ ግለሰብ የእጅ ቦምብ ወርውሮ ሊያመልጥ ሲል እርምጃ የተወሰደበት።