ኮሮናቫይረስ

በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓታት 1 ሺህ 778 ሰዎች ቫይረሱ ሲገኝባቸው 20 ሰዎች ህይወት አልፏል

By Meseret Demissu

August 20, 2020

አዲስ አበባ ፣ ነሃሴ 14፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 21 ሺህ 456 የላብራቶሪ ምርመራ 1 ሺህ 778 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።

በዚህም በኢትዮጵያ ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 35 ሺህ 836 መድረሱንም የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ ባወጡት መረጃ አመላክተዋል።