አዲስ አበባ ፣ ነሃሴ 15፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በተፋሰሱ ሀገራት ከሚገኙ የዳያስፖራ አባላት ማህበረሰብ ጋር በታላቁ ህዳሴ ግድቡ ድጋፍ ዙሪያ ውይይት መካሄዱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለፀ።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባዩ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ገዱ አንዳርጋቸው በሀገራቱ ካሉ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ጋር በግድቡ ድጋፍ ዙሪያ ውይይት ማካሄዳቸውን ገልጸዋል።