የሀገር ውስጥ ዜና

ሲሜንቶ ለመግዛት ዘጠኝ ወር ወረፋ እንደሚጠብቁ የአማራ ክልል የስሚንቶ ነጋዴዎች ገለፁ

By Tibebu Kebede

December 19, 2019

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 8 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የአማራ ክልል ንግድና ገቢያ ልማት ቢሮ በሲሜንቶ ምርት ግብይት ላይ በሚስተዋሉ ችግሮች ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አካሂዷል።

በውይይቱ የፌዴራል ንግድ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ እሽቴ አስፋው ፣ የአማራ ክልል ንግድና ገቢያ ልማት ቢሮ ምክትል ሃላፊ አቶ ተዋቸው ወርቁ ፣ የሲሜንቶ ፋብሪካ ሃላፊዎችና የአማራ ክልል ሲሜንቶ ነጋዴዎች ተገኝተዋል።