አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 8 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የብሄራዊ የመረጃና ደህንነት አገልግሎት እያካሄደ ያለው ሪፎርም ተልዕኮውንና የስራ ባህሪውን ግምት ውስጥ በማስገባት ግልፅነትና ተጠያቂነት የሰፈነበት ፕሮፌሽናል ተቋም በመመስረት ላይ እንደሚገኝ አስታውቋል፡፡
የብሄራዊ የመረጃና ደህንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ጄኔራል ኮሚሽነር ደመላሽ ገብረሚካኤል የተቋሙን የ100 ቀን እቅድ አፈጻጸም በተገመገመበት ወቅት አገልግሎት መስሪያ ቤቱ መንግስት ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት ባካሄደው የሪፎርም ስራ ተቋሙን እንደገና ለማቋቋም የሚያስችል ረቂቅ አዋጅ አጠናቋል ብለዋል፡፡