የሀገር ውስጥ ዜና

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ከሱዳኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሀምዶክ ጋር ተወያዩ

By Tibebu Kebede

August 25, 2020

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 19፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ከሱዳኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሀምዶክ ጋር ተወያይተዋል።

በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የተመራ የልኡካን ቡድን በትናትናው ዕለት ይፋዊ የስራ ጉብኝት ማድረጉ የሚታወስ ነው።