የሀገር ውስጥ ዜና

ኢትዮጵያና የሳዑዲ አረቢያ የልማት ፈንድ የ140 ሚሊየን ዶላር የብድር ስምምነት ተፈራረሙ

By Tibebu Kebede

December 19, 2019

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 9፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ኢትዮጵያ እና የሳዑዲ አረቢያ የልማት ፈንድ የ140 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር የብድር ስምምነት በዛሬው እለት ተፈራርመዋል።

የብድር ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ እና የሳዑዲ አረቢያ የልማት ፈንድ ምክትል ሊቀ መንበር ካሊድ አልክሁድራ ናቸው የተፈራረሙት።