Law and Justice concept. Mallet of the judge, books, scales of justice. Gray stone background, reflections on the floor, place for typography. Courtroom theme.

የሀገር ውስጥ ዜና

በአርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ የግድያ ወንጀል የተጠረጠረው ከበደ ገመቹ ዛሬ ለአራተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀርቧል

By Tibebu Kebede

August 25, 2020

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 19፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ የግድያ ወንጀል የተጠረጠረውና ሸሽቶ በነበረበት አዳአ ድሬ ተብሎ በሚጠራ አካባቢ ሃምሌ 3 ቀን 2012 ዓ.ም በቁጥጥር ስር የዋለው ከበደ ገመቹ ዛሬ ለአራተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀርቧል።

በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አረዳ ምድብ ተረኛ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት መርማሪ ፖሊስ ከዚህ በፊት በተሰጠው ተጨማሪ ጊዜ በተጠርጣሪው ላይ በርካታ የምርመራ ስራ ማከናወኑን ለችሎቱ አስረድቷል።