የሀገር ውስጥ ዜና

ጠ/ሚ ዐቢይ በሱዳን ቆይታቸው የተሳካ ዲፕሎማሲያዊ ስራ አከናውነዋል – የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር

By Tibebu Kebede

August 26, 2020

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 20፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በሱዳን በነበራቸው የስራ ጉብኝት ህዳሴ ግድብን ጨምሮ በሌሎች የሁለትዮሸ ጉዳዮች ላይ ስኬታማ የዲፕሎማሲ ስራ ማከናወናቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ገዱ አንዳርጋቸው ተናገሩ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሱዳን የነበራቸውን የአንድ ቀን የስራ ጉብኝት አጠናቀው ወደ አዲስ አበባ ተመልሰዋል።