የሀገር ውስጥ ዜና

የመንግስት ዓላማ ለእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ንጋትን ማብሰር ነው – ጠ/ሚ ዐቢይ

By Tibebu Kebede

August 26, 2020

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 20፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የመንግስት ዓላማ ለእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ንጋትን ማብሰር ፤ ግቡም ለሁሉም ሕዝብ ብሩህ ቀን እንዲመጣለት ማስቻል መሆኑን አስታወቁ።

በፌስቡክ ገፃቸው ባሰፈሩት ፅሁፍ የብልጽግና መንገድ የማለዳውን ጀምበር ተከትሎ እየፈካ መጥቷል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የብርሃን ጸዳሎቹ ሙቀትና ፍካትን እያጎለበቱ ለብዙዎች ተስፋን መፈንጠቃቸውን ቀጥለዋል ብለዋል።