የሀገር ውስጥ ዜና

ኢንጂነር ታከለ ኡማ ከጉራጌ ልማት ማህበር አባላት ጋር ተወያዩ

By Tibebu Kebede

December 19, 2019

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 9፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ በደቡብ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ርስቱ ይርዳ ከተመራው የጉራጌ የልማት ማህበር አባላት ጋር ተወያይተዋል።

የጉራጌ ልማት ማህበር አባላት በከተማዋ አጠቃላይ የልማት እንቅስቃሴ ላይ ተሳትፎ ለማድረግ በሚችሉበት ሁኔታ ዙሪያ ነው ውይይቱ የተደረገው።