የሀገር ውስጥ ዜና

የአዲስ አበባ ከተማ የሰላም ምክር ቤት ተመሰረተ

By Meseret Demissu

August 27, 2020

የአዲስ አበባ ከተማ የሰላም ምክር ቤት ተመሰረተ

አዲስ አበባ፤ ነሀሴ 21 ፣2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሰላም ምክር ቤት ዛሬ ተመሰረተ።

ምክር ቤቱ በአዲስ አበባ ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን፣ የሚከሰቱ ግጭቶችና አለመግባባቶችን ቀድሞ ለመከላከል፣ የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ እና ግጭቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ህብረተሰቡን በማሳተፍ የነዋሪውን የሰላም ባለቤትነት ለማረጋገጥ የተቋቋመ መሆኑ ተገልጿል።