የሀገር ውስጥ ዜና

በቀጣይ አመት በኦሮሚያ ክልል 300 መቶ ሺህ ሄክታር መሬት በስንዴ እንደሚለማ ተገለጸ

By Meseret Demissu

August 30, 2020

አዲስ አበባ ፣ ነሀሴ 24 ፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በቀጣይ አመት በኦሮሚያ ክልል 300 መቶ ሺህ ሄክታር የሚሆን መሬት በስንዴ እንደሚለማ የኦሮሚያ ግብርና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ አስታወቀ።

በዚህም ከሚለማው መሬት 26 ሚሊየን ኩንታል ምርት ለማግኘት እንደታቀደ የክልሉ ግብርና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ ሃላፊ አቶ ዳባ ደበሌ ገልጸዋል።