የሀገር ውስጥ ዜና

የጠነከረች ኢትዮጵያን ለመገንባት ተቃራኒ ዋልታዎች ላይ የሚንጠለጠሉ ፍላጎቶች መቀራረብ አለባቸው-ጠ/ሚ ዐቢይ

By Feven Bishaw

September 01, 2020

አዲስ አበባ፣ ነሀሴ 26፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የጠነከረች ኢትዮጵያን ለመገንባት በሚደረገው የብልጽግና ጉዞ አዎንታዊ ሚና መወጣት እንደሚገባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አሳሰቡ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፌስቡክ ገፃቸው ባሰፈሩት ፅሁፍ እንደ ሀገር የጋራ ግብ ከያዝን የሀገራችን ህልውና ጠብቀን የጋራ ድል እንደምንቀዳጅ ምንም ጥርጥር የለውም ብለዋል፡፡