የሀገር ውስጥ ዜና

በመጪዎቹ ሳምንታት ኢትዮጵያን ጨምሮ በምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ከፍተኛ መጠን ያለው ዝናብ ይጠበቃል

By Tibebu Kebede

September 01, 2020

አዲስ አበባ፣ ነሀሴ 26፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በመጪዎቹ ሳምንታት ኢትዮጵያን ጨምሮ በምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ከፍተኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚጠበቅ የምስራቅ አፍሪካ የአየር ንብረት የልህቀት ማዕከል አስታወቀ።

በተለይም በአብዛኛዎቹ ሰሜን ምዕራብ ኢትዮጵያ እና ሰሜን ምዕራብ ደቡብ ሱዳን አካባቢዎች ከ 200 ሚሊ ሜትር በላይ የሆነ ከባድ ዝናብ እንደሚጠበቅ ማዕከሉ አሳስቧል።