ቴክ

ፌስቡክ እና ትዊተር ሩሲያ ለምትፈፅመው የምርጫና ሌሎች ጣልቃ ገብነት የተፈጠሩ ናቸው ያሏቸውን ገፆች ዘጉ

By Meseret Demissu

September 02, 2020

አዲስ አበባ ፣ ነሀሴ 27 ፣2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ)ፌስቡክ እና ትዊተር ሩሲያ ለምትፈፅመው የምርጫና ሌሎች ጣልቃ ገብነት የተፈጠሩ ናቸው ያሏቸውን ገፆች መዝጋታቸውን አስታወቁ።

ዘመቻው ለሩስያ መንግስት ቅርብ ከሆነውና በአውሮፓውያኑ 2016 በአሜሪካ ምርጫ ጣልቃ ገብቷል ተብሎ ከሚከሰሰው የሩስያ የበይነ መረብ ምርምር ኤጀንሲ (አይ አር ኤ) ጋር የተያያዘ መሆኑም ተመላክቷል።