የሀገር ውስጥ ዜና

ባለፉት 24 ሰዓታት 1 ሺህ 105 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ሲገኝባቸው፤ የ18 ሰዎች ሕይወት አልፏል

By Tibebu Kebede

September 02, 2020

አዲስ አበባ፣ ነሀሴ 27፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 21 ሺህ 360 የላብራቶሪ ምርመራ 1 ሺህ 105 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።

በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 54 ሺህ 409 መድረሱንም ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ በፌስቡክ ገፃቸው ያወጡት መረጃ ያመለክታል።