ኮሮናቫይረስ

የኮሮና ቫይረስ የምርመራ ውጤትን በእጅ ስልክ በጽሁፍ መልዕክት ለማሳወቅ የሚያስችል አሰራር ተጀመረ

By Tibebu Kebede

September 03, 2020

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 28፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኮሮና ቫይረስ የላቦራቶሪ ምርመራ ውጤት ለተመርማሪዎች በ8335 በእጅ ስልካቸው የጽሁፍ መልዕክት እንዲደርሳቸው የሚያስችል ስራ መጀመሩን የኢትዮጵያ የሕብረተስብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታወቀ።

በኢንስቲትዩቱ የሕብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋ ማስተባበሪያ ማዕከል የዲጂታላዜሺን የስራ ክፍል የኮሮና ቫይረስ የላቦራቶሪ ምርመራ ውጤት በተቀላጠፈ መንገድ ለተመርማሪዎች ተደራሽ ከማድረግ አንጻር ኤሌክትሮኒካል በማድረግ የቫይረሱን የላቦራቶሪ ውጤት በእጅ ስልካቸው እንዲደርሳቸው እየተደረገ መሆኑን ገለጸ።