አዲስ አበባ ፣ ነሀሴ 28 ፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በተያዘው የ2013 በጀት አመት ከአገራዊ ወጪ ንግድ 3 ነጥብ 91 ቢሊየን የአሜሪካን ዶላር ለማግኘት በእቅድ መያዙን የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታውቋል።
ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ድጋፍና ክትትል ከሚያደርግባቸው የግብርና የማኑፋክቸሪንግ ምርቶች ውስጥ 2 ነጥብ 918 ቢሊየን ከግብርና እና 587 ነጥብ 5 ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር የሚሆነውን ደግሞ ከማኑፋክቸሪንግ እንደሚጠብቅ አስታውቋል።