የሀገር ውስጥ ዜና

አዲስ ዓመትን ተከትሎ የአትክልትም ሆነ የመሰረታዊ ሸቀጦች አቅርቦት እጥረት እንደማይኖር ተገለጸ

By Meseret Demissu

September 03, 2020

አዲስ አበባ ፣ ነሀሴ 28 ፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ)አዲስ ዓመትን ተከትሎ የአትክልትም ሆነ የሌሎች መሰረታዊ ሸቀጦች የአቅርቦት እጥረት እንደማይኖር የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታወቀ።

ከንግድ እና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት የተወጣጣ ቡድን በመዲናዋ የአትክልትና ፍራፍሬ እንደሁም የመሰረታዊ ሸቀጥ አቅርቦትን በተመለከተ በተለያዩ ቦታዎች ተዘዋውረው ተመልክተዋል።