አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 28፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በ2013 አዲስ ዓመት ለህዝቦች የአደረጃጀት ጥያቄዎች ሰላማዊ መሆነ መንገድ መልስ ለመስጠት እንደሚሰራ የደቡብ ክልል ምክትል ርእሰ መስተዳድር አቶ ርስቱ ይርዳው ገለፁ።
ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ቆይታ ያደረጉት ምክትል ርእሰ መስተዳድር አቶ ርስቱ ይርዳው፥ የተጠናቀቀው በጀት ዓመት የክልሉን ሰላምና መረጋጋት በማስጠበቅ ህዝቡ ወደ ልማት ስራዎች ፊቱን እንዲያዞር ለማደረግ ተሰርቷል ብለዋል።