የሀገር ውስጥ ዜና

ዓለም አቀፉ የትምህርት አጋርነት በኢትዮጵያ የትምህርት ስርዓቱን ለመደገፍ 15 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ አደረገ

By Tibebu Kebede

September 04, 2020

አዲስ አበባ፣ ነሀሴ 29፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ዓለም አቀፉ የትምህርት አጋርነት ከኮቪድ 19 ጋር ተያይዞ በኢትዮጵያ የትምህርት ስርዓቱን ለመደገፍ 14 ነጥብ 8 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ድጋፍ አደረገ።

በዓለም አቀፉ የትምህርት አጋርነት የተደረገው ድጋፍ የኮሮና ቫይረስ በትምህር ስርዓቱ ላይ ላስከተለው ችግር ምላሽ ለመስጠት መሆኑን ከዓለም ባንክ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።