የሀገር ውስጥ ዜና

በህጋዊ ንግድ ሽፋን ሊጭበረበር የነበረ ከ4 ነጥብ 4 ሚሊየን ብር በላይ ቀረጥና ታክስ ተሰበሰበ

By Feven Bishaw

September 04, 2020

አዲስ አበባ፣ ነሀሴ 29፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በህጋዊ ንግድ ሽፋን ሊጭበረበር የነበረ ከ4 ነጥብ 4 ሚሊየን ብር በላይ ቀረጥና ታክስ መሰብሰቡን የገቢዎች ሚኒስቴር አስታወቀ።

የንግድ ማጭበርበሮቹ በቦሌ፣ አዳማ፣ ቃሊቲ እና ድሬዳዋ በሚገኙ የጉምሩክ ቅርንጫፎች ተደርሶባቸው የተሰበሰቡ መሆናቸው ታውቋል።