የሀገር ውስጥ ዜና

በአማራ ክልል ወጣቶች በተገቢው መንገድ ለስራ ዕድል ፈጠራ የሚሆን ብድር እያገኘን አይደለም ሲሉ ቅሬታ አቀረቡ

By Tibebu Kebede

September 04, 2020

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 29፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በአማራ ክልል ወጣቶች በተገቢዉ መንገድ ለስራ ዕድል ፈጠራ የሚሆን ብድር እያገኘን አይደለም ሲሉ ቅሬታ አቅርበዋል፡፡

ከ2009 ዓ.ም ጀምሮ ለወጣቶች የስራ ዕድል ፈጠራ የፌዴራል መንግስት 3 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር በአማራ ክልል ለሚገኙ ወጣቶች እና ስራ ፈላጊዎች ተሰራጭቶ ወደ ስራ ገብተው ቆይተዋል፡፡