የሀገር ውስጥ ዜና

ለወባ በሽታ መከሰት ምቹ የአየር ሁኔታ በመኖሩ በሽታው በሚከሰትባቸው አካባቢዎች የሚኖር ህብረተሰብ ጥንቃቄ ሊያደርግ ይገባል- የጤና ሚንስቴር

By Tibebu Kebede

September 04, 2020

አዲስ አበባ፣ ነሀሴ 29፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በመጪ ወራት ለወባ በሽታ መከሰት ምቹ የአየር ሁኔታ በመኖሩ በሽታው በሚከሰትባቸው አካባቢዎች የሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ የጤና ሚንስቴር አሳሰበ።

የሚንስቴሩ የብሄራዊ የወባ ፕሮግራም አስተባባሪ መብራህቶም ሃይለ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደተናገሩት፥ የብሄራዊ ሜትሮሎጂ ትንበያን መሰረት በማድረግ ዝናባማ የአየር ጠባዩ እስከ መስከረም አጋማሽ ሊቆይ ስለሚችልና ይህም ለወባ ትንኝ መፈልፈያ የሚሆኑ የተቋጠሩ ውሃዎችን ሊፈጥር ስለሚችል ጥንቃቄ እንዲደረግ አስገንዝበዋል።