አዲስ አበባ፣ ነሀሴ 29፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ በተደረገው 23 ሺህ 712 የላብራቶሪ ምርመራ 1 ሺህ 303 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።
በዚህም በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 56 ሺህ 516 መድረሱንም የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ በፌስቡክ ገፃቸው ላይ ያወጡት መረጃ ያመለክታል።