አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 1፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ)”ከጳጉሜን እስከ ጳጉሜን እንደርሳለን” በሚል የተዘጋጀው ሀገር አቀፍ የመንገድ ደህንነት ንቅናቄ በይፋ ተጀመረ፡፡
ንቅናቄው በይፋ በተጀመረበት ወቅት ትራንስፖርት ሚኒስትሯ ወይዘሮ ዳግማዊት ሞገስ ቀኑ በትራንስፖርት እይታ እና አጠቃቀማችን ላይ ያካሄድ ለውጥ የምንጀምርበት እና ለዜጎች በይበልጥ ፋይዳ እንደሚጨምር የሚጠበቀው የሞተር አልባ ትራንስፖርት በሰፊው ወደ ስራ የምናስገባበት ነው ብለዋል፡፡