የሀገር ውስጥ ዜና

“ከጳጉሜን እስከ ጳጉሜን እንደርሳለን” በሚል የተዘጋጀው ሀገር አቀፍ የመንገድ ደህንነት ንቅናቄ በይፋ ተጀመረ

By Feven Bishaw

September 06, 2020

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 1፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ)”ከጳጉሜን እስከ ጳጉሜን እንደርሳለን” በሚል የተዘጋጀው ሀገር አቀፍ የመንገድ ደህንነት ንቅናቄ በይፋ ተጀመረ፡፡

ንቅናቄው በይፋ በተጀመረበት ወቅት ትራንስፖርት ሚኒስትሯ ወይዘሮ ዳግማዊት ሞገስ ቀኑ በትራንስፖርት እይታ እና አጠቃቀማችን ላይ ያካሄድ ለውጥ የምንጀምርበት እና ለዜጎች በይበልጥ ፋይዳ እንደሚጨምር የሚጠበቀው የሞተር አልባ ትራንስፖርት በሰፊው ወደ ስራ የምናስገባበት ነው ብለዋል፡፡