የሀገር ውስጥ ዜና

የቀድሞ የሃዋሳ ጨርቃጨርቅ ፋብሪካ በ2 ቢሊየን ብር ወጪ ወደ ግዙፍ ኢንደስትሪ መንደርነት ሊያድግ ነው

By Feven Bishaw

September 06, 2020

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 1፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ)የቀድሞ የሃዋሳ ጨርቃጨርቅ ፋብሪካ በ2 ቢሊየን ብር ወጪ ወደ ግዙፍ ኢንደስትሪ መንደርነት ሊያድግ ነው፡፡

ፋብሪካው ወደ ጨርቃጨርቅና ኢንደስትሪ ፓርክ ለሚያደርገው ሽግግር ዛሬ ተጨማሪ የማምረቻ ሼዶች ግንባታ ማስጀመሪያ ስነ-ስርዓት በይፋ ተከናውኗል፡፡