አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 1፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ)በከተማ ደረጃ የይቅርታ ቀን በተለያዩ ዝግጅቶች ተከብሮ ውሏል።
በመርሃ ግብሩ ላይ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴን ጨምሮ ምክትል ከንቲባ አዳነች አቤቤ ፣ የሀይማኖት አባቶች፣ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የተገኙ ሲሆን ፕሬዚዳንቷ የይቅርታ ዝግጅቱ ወቅታዊ እና አስፈላጊ ነው ፤ ይቅርታ በመደራረግ ማህበራዊ እሴቶቻችንን በማጎልበት አብሮነታችንን እናጽና ብለዋል፡፡