የሀገር ውስጥ ዜና

በከተማ ደረጃ የይቅርታ ቀን ተከበረ

By Feven Bishaw

September 06, 2020

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 1፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ)በከተማ ደረጃ የይቅርታ ቀን በተለያዩ ዝግጅቶች ተከብሮ ውሏል።

በመርሃ ግብሩ ላይ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴን ጨምሮ ምክትል ከንቲባ አዳነች አቤቤ ፣ የሀይማኖት አባቶች፣ የመንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የተገኙ ሲሆን ፕሬዚዳንቷ የይቅርታ ዝግጅቱ ወቅታዊ እና አስፈላጊ ነው ፤ ይቅርታ በመደራረግ ማህበራዊ እሴቶቻችንን በማጎልበት አብሮነታችንን እናጽና ብለዋል፡፡